ኢትዮጵያ ያለ እድሜ ጋብቻና የሴት ልጅ ግርዛትን ለመከላከል በሰራችው ውጤታማ ሥራ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ሥነ ሕዝብ ድርጅት እውቅና አገኘች።
የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በትናንትናው እለት በኒውዮርክ የተመድ ዋና መስሪያ ቤት ተገኝተው ሽልማቱን ተቀብለዋል፡፡
ሚኒስትሯ የኢትዮጵያ መንግስት በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችና ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለማስወገድ የወሰዳቸውን የህግ፣ የፖሊሲና የፕሮግራም እርምጃዎች አብራርተዋል።
እውቅናና ሽልማቱ መንግስት ለስርዓተ ፆታ እኩልነትና ሴቶችን ለማብቃት ያለውን ቁርጠኝነት የበለጠ የሚያጠናክር እንደሆነም ገልፀዋል፡፡
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተመድ ምክትል ዋና ፀሐፊ አሚና መሃመድ፣ የተመድ ሥነ ህዝብ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ናታኒያ ካኔምና ሌሎች የተመድ አባል ሀገራትና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች የሥራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
በኢትዮጵያ ያለ እድሜ ጋብቻና የሴት ልጅ ግርዛትን ለማስወገድ የተቋቋመው ጥምረት በፈረንጆቹ 2012 የተመሰረተ ሲሆን÷ በጥምረቱ ውስጥ የመንግስት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህበራት፣ የምርምር ተቋማትና የሃይማኖት ተቋማት ይገኛሉ፡፡
FBC
More Stories
” የፕሬስ ነጻነት ቀን ስናከብር ዜጎች በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) መረጃ እንዳይጭበረበሩ ትክክለኛ መረጃ የሚያገኙበት እሳቤ የሚያጎላበት ቀን ሊሆን ይገባል፡፡”
አራተኛው ዙር የኢራን እና የአሜሪካ ድርድር ላልተወሰነ ጊዜ ተላለፈ
የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የስራ ኃላፊዎች የማሻ ቅርንጫፍ ጣቢያ የስራ አፈጻጸምን ተመለከቱ