ኢትዮጵያ ያለ እድሜ ጋብቻና የሴት ልጅ ግርዛትን ለመከላከል በሰራችው ውጤታማ ሥራ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ሥነ ሕዝብ ድርጅት እውቅና አገኘች።
የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በትናንትናው እለት በኒውዮርክ የተመድ ዋና መስሪያ ቤት ተገኝተው ሽልማቱን ተቀብለዋል፡፡
ሚኒስትሯ የኢትዮጵያ መንግስት በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችና ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለማስወገድ የወሰዳቸውን የህግ፣ የፖሊሲና የፕሮግራም እርምጃዎች አብራርተዋል።
እውቅናና ሽልማቱ መንግስት ለስርዓተ ፆታ እኩልነትና ሴቶችን ለማብቃት ያለውን ቁርጠኝነት የበለጠ የሚያጠናክር እንደሆነም ገልፀዋል፡፡
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተመድ ምክትል ዋና ፀሐፊ አሚና መሃመድ፣ የተመድ ሥነ ህዝብ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ናታኒያ ካኔምና ሌሎች የተመድ አባል ሀገራትና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች የሥራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
በኢትዮጵያ ያለ እድሜ ጋብቻና የሴት ልጅ ግርዛትን ለማስወገድ የተቋቋመው ጥምረት በፈረንጆቹ 2012 የተመሰረተ ሲሆን÷ በጥምረቱ ውስጥ የመንግስት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህበራት፣ የምርምር ተቋማትና የሃይማኖት ተቋማት ይገኛሉ፡፡
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።