አሜሪካ እና ሩሲያ የመካከለኛ እና አጭር ርቀት የኑክሌር አረር ሚሳኤሎችን ላለማምረት ስምምነት ነበራቸው
አሜሪካ ይህንን ስምምነት በመጣስ በፊሊፒንስ እና ዴንማርክ ተመሳሳይ ሚሳኤሎችን አስፍራለች ተብሏል
ፕሬዝዳንት ፑቲን የኑክሌር አረር የታጠቁ ሚኤሎች እንዲሰሩ አዘዙ፡፡
ከሁለተኛው ዓለም ጦርነት መጠናቀቅ በኋላ ዓለማችን ከባድ የጦር መሳሪያ ማምረት ፉክክክር ውስጥ ገብታ የነበረ ሲሆን ዋነኞቹ ተፎካካሪዎች ደግሞ አሜሪካ እና ሶቪየት ህብረት ነበሩ፡፡
የወቅቱ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሮናልድ ሬገን እና የሶቭየት ህብረት ፕሬዝዳንት ሚካኤል ጎርባቾቭ መካከለኛ እና የአጭር ርቀት የሚጓዙ ኑክሌር አረር የተገጠመላቸው ሚሳኤሎችን ላለማምረት ከ37 ዓመት በፊት ስምምነት ተፈራርመው ነበር፡፡
ይሁንና ዶናልድ ትራምፕ በፈረንጆቹ 2019 ላይ ሩሲያ ይህንን ስምምነት እያከበረች አይደለም፣ አሜሪካ በዚህ ስምምነት ታጥራ እያለ ቻይና በጎን እያመረተች እና አነው በሚል ስምምነቱን በይፋ ሰርዘዋል፡፡
Al-Ain
More Stories
አሜሪካ በኢራን ላይ የአየር ጥቃት ፈፀመች
አሜሪካ በኢራን ላይ አዲስ የአየር ጥቃት ፈፀመች
በ24 ሰዓት ውስጥ 25 መርከቦች በሆርሙዝ ሰርጥ አልፈዋል – ኢራን