አርሰን ቪንገር አምባሳደር የሆኑበት ይህ ውድድር የፊታችን ነሃሴ ለሶስት ቀናት ይካሄዳልበውድድሩ ላይ አሰልጣኞች እና ተጫዋቾ ባሉበት ሆነው ይፋለሙበታል ተብሏል100 ሺህ ዶላር የሚያሸልመው አዲሱ የፊፋ የእግር ኳስ ውድድር ምንድን ነው?የዓለም እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፊፋ ከዚህ በፊት ተደርጎ የማይታወቅ ለየት ያለ ውድድር ማዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡የቀድሞው የአርሰናል እግር ኳስ ቡድን አሰልጣኝ የሆኑት አርሰን ቪንገር አምባሳደር የሆኑበት ይህ ውድድር የእግር ኳስ ጠበብቶች ባሉበት ሆነው በታክቲክ የሚፋለሙበት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡በውድድሩ ለይ በመላው ዓለም ያሉ አሰልጣኞች ወደ ፊፋ ድረገጽ በመግባት መመዝገብ በውድድሩ ለይ ለመሳተፍ የመጀመሪያው መስፈርት ነውም ተብሏል፡፡ውድድሩ ከነሀሴ 23 እስከ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ይካሄዳል የተባለ ሲሆን በፊፋ ኢስፖርት ስር መዘጋጀቱን ቪንገር ለሮይተርስ ተናግረዋል፡፡እንደ ዘገባው ከሆነ እግር ኳስ ተጫዋቾችም በፊፋ ድረገጽ ላይ ተመዝግበው በውድድሩ ላይ መካፈል ይችላሉ የተባለ ሲሆን አሰልጣኞች ከዚህ በፊት ያልሞከሯቸውን ታክቲኮች በበይነ መረብ አማካኝነት በጌም መልክ እንዲተገብሩት ያስችላቸዋልም ተብሏል፡፡
Al-Ain
More Stories
የሸካ ዞን የታዳጊ ወጣቶች የእግርኳስ ቡድን የ2018 ክልል አቀፍ ውድድር የዋንጫ አሸናፊ ሆነ።
5ተኛው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር፣ የባህል ፌስቲቫል እና የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የታለመውን ግብ ያሳካ መሆኑ ተገለጸ።
ባካሪ ሳኛ ኢትዮጵያ ገባ