በ17ኛው የአውሮፓ ዋንጫ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ስፔን ጅርጂያን 4 ለ 1 በመርታት ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለች። ከምሽቱ 4 ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ በምድብ ሁለት ዘጠኝ ነጥብ በመያዝ በአንደኛ ደረጃ ጥሎ ማለፉን የተቀላቀለችው ስፔን በአውሮፓ ዋንጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፈችውንና ከምድብ ስድስት በ4 ነጥብ ምርጥ ሶስተኛ ሆና ጥሎ ማለፉን የተቀላቀለችውን ጆርጂያን አሸንፋለች። ስፔን በሩብ ፍጻሜው ከአዘጋጇ ጀርመን ጋር ትጫወታለች። በጥሎ ማለፉ በተደረጉ ጨዋታዎች ስዊዘርላንድ፣ ጀርመን፣ እንግሊዝ እና ስፔን እስካሁን ሩብ ፍጻሜውን የተቀላቀሉ ሀገራት ሆነዋል።
ስፔን ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለች
More Stories
ሪያል ማድሪድ የዓለማችን ውዱ ክለብ ሆነ
ፒኤስጂ በተከታታይ ለ2ኛ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን አሸነፈ
ክሪስታል ፓላስ የአውሮፓ ኮንፍረንስ ሊግ ሻምፒዮን ሆነ!