የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከናይጄሪያ ፌዴራል ሪፐብሊክ የጦር ኮሌጅ ጋር “የማዕድን ዘርፍን መጠበቅ ለተጠናከረ ብሔራዊ ደህንነት” በሚል ርዕስ የልምድ ልውውጥ አድርጓል፡፡
በልምድ ልውውጡ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ÷ ኢትዮጵያ በርካታ ማዕድናት እንዳላት በመግለጽ የመንግስት ፖሊሲና መመሪያ በመሻሻሉ ምክንያትም ለልማት ከፍተኛ አቅም መፍጠሯን ገልፀዋል።
ኢትዮጵያ በሀገርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማዕድን አምራች ባለሃብቶች ማራኪ መዳረሻ መሆኗን ጠቅሰዋል፡፡
ሀብቶችን ከሕገ-ወጥ ብዝበዛና ከሕገ-ወጥ ዝውውር መጠበቅ ለሀገር ደኅንነት ወሳኝ ሚና እንዳለውም አንስተዋል፡፡
ሕገ-ወጥ የማዕድን ሥራ ግጭትን እንዳያባብስ፣ የተደራጁ ወንጀሎችን ተጠናክረው በአካባቢው ማህበረሰብ ሕይወት ላይ ተጽዕኖ እንዳያሳድሩ ፖሊስ ለዘርፉ ትልቅ ትኩረት በመስጠት ኃላፊነት ያለው አስተዳደር ለማረጋገጥ እየሠራ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡
በናይጄሪያ የፌደራል ሪፐብሊክ ጦር ኮሌጅ አዛዥ ሜጀር ጀነራል አይቢ ማይና የተመራው ልዑካን ቡድን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የቴክኖሎጂ አቅሞችን ተዘዋውሮ መጎብኘቱን ከፌዴራል ፖሊስ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።