የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ ስራዎች እየተሰሩ ቢሆንም የችግሩ አሳሳቢነት ግን እየከፋ መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡
የመንገድ ደህንነትን ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን ያደረገ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው።
በምክክር መድረኩ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ÷በኢትዮጵያ የትራፊክ አደጋ የሰው ህይወትን በመቅጠፍ፣አካል በማጉደል እና ንብረትን በማውደም ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን ተናግረዋል።
የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ ስራዎች እየተሰሩ ቢሆንም የችግሩ አሳሳቢነት ግን እየከፋ መሆኑን ገልፀዋል።
በመሆኑም ይህን ችግር ለመከላከል በቅንጅት በመስራት መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በውይይቱ የክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የመንገድ ደህንነት ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ሲሆን÷ የትራፊክ አደጋን መከላከል ያልተቻለባቸውን ምክንያቶች በመለየት መሠራት ያለባቸው የመፍትሄ ሀሳቦች እንደሚቀመጡ ተገልጿል።
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።