የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኢትዮጵያ የኦስትሪያ ሪፐብሊክ አምባሳደር ሲሞን ክናፕ ጋር በኢትዮጵያና ኦስትሪያ መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል፡፡
አምባሳደር ምስጋኑ የሀገራቱ ታሪካዊ ግንኙነት በተለያዩ መስኮች በተለይም በኢኮኖሚው ዘርፍ የበለጠ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
አምባሳደር ክናፕ በበኩላቸው÷ የኦስትሪያ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ እንዲሁም የኦስትሪያ የቢዝነስ ልዑካን ቡድን በመጭው ጥቅምት ወር በኢትዮጵያ ጉብኝት ለማድረግ ያለውን እቅድ አብራርተዋል።
ሁለቱ ወገኖች በኦስትሪያ የንግድ ተቋማት እና በኢትዮጵያውያን አቻዎቻቸው መካከል የልምድ ልውውጥ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን መጠቆማቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
የኢትዮጵያ ማዕድን ሚኒስቴርንና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን በኦስትሪያ ከሚገኙ የሚመለከታቸው አካላት ጋር በማስተሳሰር በማዕድን ዘርፍ የተሰማሩ ኢትዮጵያውያንን አቅም ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ላይም ተወያይተዋል።
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።