ያሳለፍነው አርብ ዕለት በታሪክ ብዙ መንገደኞች የተስተናገዱበት ዕለት ሆኖ ተመዝግቧል
የአሜሪካ አቪዬሽን ባለስልጣን በቀጣዮቹ ሶስት ወራት ውስጥ 271 ሚሊዮን መንገደኞችን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል
የአሜሪካ ኤርፖርቶች በአንድ ቀን ብቻ ሶስት ሚሊዮን መንገደኞችን አስተናገዱ፡፡
በአሜሪካ የክረምት ወራት የሚጀመርበት ወቅት መድረሱን ተከትሎ አየር መንገዶች በመንገደኞች ብዛት እየተጥለቀለቁ ይገኛሉ፡፡
ያሳለፍነው አርብ ዕለትም ብቻ የአሜሪካ ኤርፖርቶች 2 ነጥብ 9 ሚሊዮን መንገደኞችን እንዳስተናገዱ ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
እንደ ኒዮርክ አይነት ብዙ በረራ የሚደረግባቸው ከተሞች በአየር ተቆጣጣሪ ባለሙያዎች እጥረት ምክንያት በረራዎችን ሰርዘዋል ተብሏል፡፡
እንደ ዘገባው ከሆነ በአንድ ቀን በረራ ያደረጉ መንገደኞች ቁጥር በታሪክ ከፍተኛው ዕለት ሆኖ የተመዘገበ ሲሆን የመንገደኞች ቁጥር እየጨመረ እንደሚሄድ ይጠበቃልም ተብሏል፡፡
More Stories
የአውሮፓ ህብረት ያወጣቸውን ደንቦች መሠረት በማድረግ የግብርና ምርቶች ከደን ጭፍጨፋ ነፃ ሆነው እንዲመረቱ ከማድረግ አንፃር የግብርና ባለሙያዎች ሚና የጎላ እንደሆነ ተገለፀ ።
ትራምፕ ቲክ ቶክን የሚገዙ የአሜሪካ ባለሀብቶች ማግኘታቸውን ገለፁ
ሩሲያ እና ህንድ በጦር መሳሪያ አቅርቦት ላይ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ እንደሚሰሩ አስታወቁ፡፡