በ16 ተሽከርካሪ ወደ መሀል ሀገር ሊገቡ የተዘጋጁ 525 ሚሊየን 245 ሺህ ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች በትናንትናው ዕለት በሶማሌ ክልል ቢዮባሃይ በተባለ አካባቢ ተያዙ፡፡
የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ ሊያዙ የቻሉት የሶማሌ ክልል መንግሥት የፀጥታ አካላት፣ የሀገር መከላከያ እና የፌደራል ፖሊስ ከጉምሩክ ኮሚሽን ጋር ባደረጉት የተቀናጀ ክትትል መሆኑ ተገልጿል፡፡
ከተያዙት የኮንትሮባንድ ዕቃዎች መካከልም አልባሳት፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎች፣ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ መድኃኒት፣ ሲጋራ፣ የቤት ክዳን ቆርቆሮ እና ሌሎችም ይገኙበታል ተብሏል፡፡
በድርጊቱ የተሳተፉ አካላትን በቁጥጥር ሥር ለማዋል የክትትል ሥራዎች ተጠናክረው መቀጣላቸውን የጉምሩክ ኮሚሽን መረጃ አመላክቷል፡፡
EBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።