አምባሳደር ኢርቪን ማሲንጋ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ያነሷቸው ወቀሳዎች በተሳሳቱ መረጃዎች ላይ የተመሰረተ ነው ብሏል የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
አምባሳደሩ በኢትዮጵያ የንጹሃን ግድያ፣ ያለህጋዊ አግባብ የሚፈጸም እስርና ስወራ በአፋጣኝ እንዲቆም ማሳሰባቸው ይታወሳል
አምባሳደር ኢርቪን ማሲንጋ ትናንት በአሜሪካ ግቢ ባደረጉት “የሰብአዊ መብትና ምክክር የፖሊስ ንግግር” ያነሷቸው ወቀሳዎች በሀሰተኛ መረጃ የተመሰረተ ነው ብሏል የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በዛሬው እለት ባወጣው መግለጫ።
አምባሳደር ኢርቪን “ኢትዮጵያ ሳትጠይቃቸው የውስጥ ችግሯን እንዴት ትፍታው የሚል ምክርን ሲለግሱ ታይተዋል” የሚለው መግለጫው፥ በምርጫ ስልጣን ላይ ያለውን የኢትዮጵያ መንግስት ንጹሃንን ከሚያግቱና ከሚያሸብሩ አካላት ጋር መጥቀሳቸውም ተገቢ አለመሆኑን አብራርቷል።
Al-Ain
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።