በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል 348 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ መቅረቡን የክልሉ ማዕድን እና ኢነርጂ ኤጀንሲ አስታወቀ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰሞኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በወርቅ ምርት እመርታዊ ውጤት መመዝገቡን መግለጻቸው ይታወሳል።
በዚህም በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ከወርቅ ማዕድን ምርት 5 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ገቢ ማገኘት የሚያስችል አቅም መፈጠሩን ጠቅሰው፣ ኢትዮጵያ በብዝሀ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ለማዕድን ዘርፍ የሰጠችው ትኩረት ውጤቱን ከፍ ማድረጉንም ተናግረዋል።
የወርቅ ማዕድን ከሚመረትባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች አንዱ በሆነው ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልልም ለዘርፉ በተሰጠ ትኩረት የወቅር ምርት በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መጥቷል።
ኢዜአ ያነጋገራቸው የክልሉ ማዕድንና ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ጌታቸው ወልያብ (ዶ/ር) እንዳሉት፣ በክልሉ በበጀት ዓመቱ የተመዘገበው የወርቅ አቅርቦት ምጣኔ ከፍተኛ ነው።
ለእዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 350 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ለማቅረብ ታቅዶ 348 ኪሎ ግራም ምርት መቅረቡን በማሳያነት ተናግረዋል።
አፈጻጸሙ በ2017 በጀት ዓመት ከክልሉ ከቀረበው 155 ነጥብ 5 ኪሎ ግራም የወርቅ ምርት አንጻር ሲታይ በከፍተኛ መጠን ጭማሪ ማሳየቱንም ገልጸዋል።
የለውጡ መንግስት ለማዕድን ዘርፍ በሰጠው ትኩረትና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ባደረጉት ጠንካራ ክተትል የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉንም ጠቁመዋል።
በ2019 በጀት ዓመትም ከዘንድሮ ከፍ ያለ የወርቅ መጠን ለብሔራዊ ባንክ በማቅረብ ሀገራዊ የውጭ ምንዛሬ አቅምን በማጠናከር በኩል ክልሉ ያለውን ሚና እንዲያሳድግ ቅንጅታዊ አሰራር ይጠናከራል ብለዋል።
ለዚህም ተደራጅተው ፈቃድ ያገኙ ወርቅ አምራች ማኅበራት በመሉ አቅም ወደ ተግባር እንዲገቡ በማድረግና አዳዲስ ማኅበራትን በማሰማራት የዘርፉን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለማስቀጠል እንደሚሰራ ተገልጿል።
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከክልሉ 348 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ቀርቧል
More Stories
ኢትዮጵያ ለኬንያ 1 ኪሎ ዋት ሰዓት ኢነርጂ በ24 ብር ከ07 ሳንቲም ለማቅረብ ተስማማች
አሜሪካና ኢራን አያቶላ አሊ ኻሜኒ በሚቀበሩበት ወቅት የጀመሩት ጥቃቶች ተጠናክረው ቀጠሉ ።
በበጀት ዓመቱ የንግዱን ዘርፍ በቴክኖሎጂ በማገዝ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል – ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)