July 11, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

አሜሪካና ኢራን አያቶላ አሊ ኻሜኒ በሚቀበሩበት ወቅት የጀመሩት ጥቃቶች ተጠናክረው ቀጠሉ ።

የቀድሞው የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ አስከሬን በኢራቅ ናጃፍ ከተማ የቀብር ሥነ-ሥርዓት በክብር እየተከናወነ ባለበት ወቅት አሜሪካ እና ኢራን  አዲስ ጥቃት ከፍተዋል።
‎ታዛቢዎች በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል የሚጓዙ መርከቦች ቁጥር “በአስደናቂ ሁኔታ ቀንሷል” ሲሉ ሪፖርት አድርገዋል።

‎አሜሪካ 90 ወታደራዊ ኢላማዎችን መምታቷን ስትገልጽ፥ አንዳንዶቹ በባሕረ ሰላጤው አቅራቢያ የተፈጸሙ ናቸው ተብሏል።
‎ኢራን ባለፉት ሁለት ቀናት ውስጥ ብቻ14 ሰዎች መገደላቸውን አስታውቃለች።

‎የመንግስት ሚዲያዎች እንደዘገቡት የቡሼህር የኑክሌር ኃይል ማመንጫ አቅራቢያ የጥቃቶቹ ኢላማ መሆኑ ተነግሯል።

‎አሜሪካ አዲሱን ጥቃት በተመለከተ አስያያየት ከመስጠት ተቆጥባለች።
‎ኢራን በአጸፋው በኩዌት፣ ባህሬን እና ኳታር የሚገኙ የአሜሪካ ንብረቶችን ተጨማሪ ጥቃት ማድረጓን በማሳወቅ ጥቃቱንም አጠናክሬ እቀጥላለሁ ብላለች።