የቅድመ ምረቃ በረራው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ኤርፖርቶች ማኔጅንግ ዳይሬክተር አቶ ጌታነህ አደራ ጨምሮ ሌሎች የአየር መንገዱ ከፍተኛ ማኔጅመንቶች እንዲሁም የክልል፣ የቤንች ሸኮ ዞንና የሚዛን አማን ከተማ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ነው በይፋ የጀመረው።
የበረራ አገልግሎቱ መጀመር በአካባቢው ነዋሪዎች፣ ተጓዦችና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሠራተኞች ዘንድ ከፍተኛ ደስታን ፈጥሯል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሚዛን አማን ከተማ በሳምንት ሦስት ቀናት የበረራ መርሐግብር እንደሚያደርግ የተገለጸ ሲሆን፣ በረራው ለማኅበረሰቡ ፈጣን፣ ምቹና ቀልጣፋ የትራንስፖርት ጉዞ አገልግሎት ለማቅረብ ያግዛል።
በተጨማሪም የንግድ፣ የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎችን በማነቃቃት ለሚዛን አማን ከተማ ብሎም ለመላው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ለማሕበራዊ ትስስርና ኢኮኖሚ ዕድገት ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል ተብሏል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዛሬ ከሐምሌ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሚዛን አማን ከተማ የቅድመ ምረቃ በረራ ጀምሯል።
More Stories
ኢትዮጵያ ለኬንያ 1 ኪሎ ዋት ሰዓት ኢነርጂ በ24 ብር ከ07 ሳንቲም ለማቅረብ ተስማማች
በበጀት ዓመቱ የንግዱን ዘርፍ በቴክኖሎጂ በማገዝ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል – ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከክልሉ 348 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ቀርቧል