July 11, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 51ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመስተዳድር ምክር ቤት  በዛሬው ዕለት ባካሄደው 51ኛ መደበኛ ስብሰባው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል ፡፡

‎በዚህም መሠረት የቀረቡ የኢንቨስትመንት ጥያቄዎች ላይ ተወያይቶ የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን  በግብርና 18፣ በኢንዱስትሪ 1 በአጠቃላይ 2.3 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ጥያቄዎችን መርምሮ ወደ  ስራ እንዲገቡ ወስኗል።

‎በሁለተኛ አጀንዳነት በተለያዩ ረቂቅ ደንቦች ላይ የተወያየ ሲሆን በዚህም የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቨሽን ካውንስል ማቋቋሚያ ደንብን እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የአከባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ደንብን መርምሮ  አጽጽቋል።