ከእረፍትና ልዩ ልዩ ፍቃዶች ውጭ ለአምስት ተከታታይ ቀናትና ከዚያ በላይ ከስራ የቀረ ሰራተኛን ማስጠንቀቂያ መስጠት ሳያስፈልግ የሥራ ውልን ማቋረጥ የሚያስችል አዲስ የህግ ትርጉም ተሰጥቷል፡፡
የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከዚህ በፊት በሰበር መዝገብ ቁጥር 249795 ላይ አንድ ሰራተኛ በተከታታይ ከአምስት ቀናት በላይ ከሥራ ከቀረ አሰሪው ለእያንዳንዱ ቀን ማስጠንቀቂያ ሳይሰጥ የሥራ ውልን ማቋረጥ እንደማይችል ጠቅሶ የሕግ ትርጉም ሰጥቶ ነበር።
ሆኖም ሰበር ሰሚ ችሎቱ አሁን ላይ አሰሪው ለእያንዳንዱ ቀን ማስጠንቀቂያ ሳይሰጥ ከስራ ማሰናበት የለበትም የሚለውን የሕግ ትርጉም ሽሮታል።
በምትኩ ከእረፍቶችና ልዩ ልዩ ፍቃዶች ውጭ አንድ ሰራተኛ ለአምስት ተከታታይ የሥራ ቀናትና ከዚያ በላይ ከሥራ ከቀረ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ መስጠት ሳያስፈልግ የሥራ ውሉን ማቋረጥ ይቻላል የሚል ትርጉም ተሰጥቷል።
More Stories
አዛውንቶች የሚገደሉበትና ንብረት የሚዘረፍበት ተግባር የትግል ዓላማ ሊሆን አይችልም – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ የንግሥ በዓል በቁልቢ እና በሐዋሳ እየተከበረ ነው
ኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በስፋት ያሰባሰባቸው አጀንዳዎች፣ ሕዝቡ በአንድነትና በወንድማማችነት ለመኖር ያለውን የጸና ፍላጎት በግልጽ የሚያመላክቱ መሆናቸውን ምሁራን ገለጹ።