ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ዛሬ ነሀሴ 16/2018 ዓ.ም የመዝጊያ መርሃግብሩ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
ጉባኤው ለዚህ ምዕራፍ የበቃው 4ሺ ልዩ ልዩ ባለድርሻ አካላትን የወከሉ ኢትዮጵያውያን ተመካካሪዎችን በአንድ ላይ አሰባስቦ ለ38 ቀናት በተካሄደ የተቀናጀ የምክክር ሂደት ነው፡፡
በዚህ ሂደት በስምንት አጀንዳዎች ላይ ሲመክሩ የቆዩት 4ሺ ተመካካሪዎች በሀገሪቱ እጅግ መሰረታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በመከባባር፣ በመደማመጥ ተነጋግረው ምክረሃሳቦችን ለኮሚሽኑ አስረክበዋል፡፡
በዚህ የመዝጊያ ስነ-ስርዓት ላይ ተመካካሪዎች፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች እንዲሁም የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡
More Stories
የተሻለች ሀገር ለትውልድ የማሸጋገር ርዕይ – ሀገራዊ ምክክር
ወቅታዊ መረጃዎችን፣ አስተማሪና አዝናኝ ኘሮግራምችን ተደረሽ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
አዛውንቶች የሚገደሉበትና ንብረት የሚዘረፍበት ተግባር የትግል ዓላማ ሊሆን አይችልም – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)