August 22, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የመዝጊያ መርሀ ግብር

ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ዛሬ ነሀሴ 16/2018 ዓ.ም የመዝጊያ መርሃግብሩ እየተከናወነ ይገኛል፡፡

ጉባኤው ለዚህ ምዕራፍ የበቃው 4ሺ ልዩ ልዩ ባለድርሻ አካላትን የወከሉ ኢትዮጵያውያን ተመካካሪዎችን በአንድ ላይ አሰባስቦ ለ38 ቀናት በተካሄደ የተቀናጀ የምክክር ሂደት ነው፡፡

በዚህ ሂደት በስምንት አጀንዳዎች ላይ ሲመክሩ የቆዩት 4ሺ ተመካካሪዎች በሀገሪቱ እጅግ መሰረታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በመከባባር፣ በመደማመጥ ተነጋግረው ምክረሃሳቦችን ለኮሚሽኑ አስረክበዋል፡፡

በዚህ የመዝጊያ ስነ-ስርዓት ላይ ተመካካሪዎች፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች እንዲሁም የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡