በዓለም አቀፍ ደረጃ እየታየ የመጣውን የምግብ ዋስትና ስጋት ለመቀነስ እና የገበያ መረጋጋትን ለመፍጠር ሩስያ በብሪክስ ሀገራት እና በቀጣናዊ አጋሮች በጋራ የሚመራ የመጠባበቂያ ምግብ ክምችት ዘዴ እንዲመሰረት የሚያስችል ሐሳብ አቀረበች።
የሩስያ የደህንነት ምክር ቤት ከፍተኛ ባለስልጣን እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ እየተስተዋለ ያለው የነዳጅ እና የማዳበሪያ ምርት አቅርቦት መስተጓጎል በግብርናው ዘርፍ ላይ እያሳደረው ያለውን ጫና ለመቋቋም በአጋር ሀገራት መካከል ጠንካራ ቅንጅት መፍጠርን አስፈላጊ አድርጎታል።
በተለይም በመካከለኛው ምስራቅ ያገረሸው ግጭት የማዳበሪያ ንግድ ዋነኛ መስመር የሆነው የሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥ እንዲዘጋ በማድረጉ፣ ለሰብል ምርታማነት ወሳኝ በሆነው የማዳበሪያ አቅርቦት ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ ማሳረፉ ተመልክቷል።
ሩስያ ይህን ስጋት በዘላቂነት ለመቀነስ የጋራ የመጠባበቂያ ምግብ ክምችት ዘዴ እንዲኖር ሐሳብ ያቀረበች ሲሆን፣ በተጨማሪም እ.አ.አ እስከ 2030 ድረስ የግብርና ምርት ወጪ ንግዷን በ50 በመቶ በማሳደግ በዓለም አቀፍ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለት ውስጥ ተምትጫወተውን ቁልፍ ሚና ይበልጥ ለማጠናከር በቁርጠኝነት እየሠራች መሆኑን አስታውቃለች።
More Stories
የኢትዮጵያን የሰው ዘር መገኛነት ዳግም ያረጋገጡ አዲስ የአርኪዮሎጂ ግኝቶች…
በመጪዎቹ ሁለት ሳምንታት የበልግ ተጠቃሚ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ ዝናብ ያገኛሉ ተባለ
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት ውስጥ ከኢራን ጋር ድርድር ሊኖር እንደሚችል ፍንጭ ሰጡ