በዓለም አቀፍ ደረጃ እየታየ የመጣውን የምግብ ዋስትና ስጋት ለመቀነስ እና የገበያ መረጋጋትን ለመፍጠር ሩስያ በብሪክስ ሀገራት እና በቀጣናዊ አጋሮች በጋራ የሚመራ የመጠባበቂያ ምግብ ክምችት ዘዴ እንዲመሰረት የሚያስችል ሐሳብ አቀረበች።
የሩስያ የደህንነት ምክር ቤት ከፍተኛ ባለስልጣን እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ እየተስተዋለ ያለው የነዳጅ እና የማዳበሪያ ምርት አቅርቦት መስተጓጎል በግብርናው ዘርፍ ላይ እያሳደረው ያለውን ጫና ለመቋቋም በአጋር ሀገራት መካከል ጠንካራ ቅንጅት መፍጠርን አስፈላጊ አድርጎታል።
በተለይም በመካከለኛው ምስራቅ ያገረሸው ግጭት የማዳበሪያ ንግድ ዋነኛ መስመር የሆነው የሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥ እንዲዘጋ በማድረጉ፣ ለሰብል ምርታማነት ወሳኝ በሆነው የማዳበሪያ አቅርቦት ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ ማሳረፉ ተመልክቷል።
ሩስያ ይህን ስጋት በዘላቂነት ለመቀነስ የጋራ የመጠባበቂያ ምግብ ክምችት ዘዴ እንዲኖር ሐሳብ ያቀረበች ሲሆን፣ በተጨማሪም እ.አ.አ እስከ 2030 ድረስ የግብርና ምርት ወጪ ንግዷን በ50 በመቶ በማሳደግ በዓለም አቀፍ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለት ውስጥ ተምትጫወተውን ቁልፍ ሚና ይበልጥ ለማጠናከር በቁርጠኝነት እየሠራች መሆኑን አስታውቃለች።
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።