ልማት ማህበሩ የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ በሰንበት ገበያ የተለያዩ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለነዋሪዎች አቅርበዋል ።
ገቢያን ከማረጋጋት አንጻር የሰንበት ገበያ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑን የተናገሩት ሸማቾች ልማት ማህበሩ ለበዓል የሚሆን ምርት በማቅረቡ ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል ።
ማህበሩ እያቀረበ የሚገኘውን የምርት ዋጋ ያነጻጸሩት ሸማቹቾች ቀይ ሽንኩርት ገቢያ ላይ ከ1መቶ 50 እስከ 1መቶ 60ሲሆን በልማት ማህበሩ የሰንበት ገቢያ 1መቶ 10፤ ዘይት ፈሳሽ ባለ 5 ሊትር በሱቅ 2ሺህ 5መቶና ከዚያ በላይ ስሸጥ በልማት ማህበሩ 2ሺህ 2መቶ ብር እየሸመቱ መሆኑን ተናግረዋል።
ልማት ማህበሩ የጀመረውን በጎ ተግባር በሌሎችም ምርቶች ላይ አሰፍተው እንድቀጥል የገለጹት ሸማቾቹ ህብረተሰብ ከልማት ማህበሩ ጎን በቁርጠኝነት በመቆም የልማት ስራዎችን እንደሚያፋጥኑ ጠቁመዋል።
የሸካ ልማት ማህበር የፋስካ በዓል ምክንያት በማድረግ ለሸማቹ ህብረተሰብ ካቀረበው ምርቶች መካከል ቀይ ሽንኩርት፣ ዘይትና ዱቤ ዱቄት ይገኙበታል።
የሸካ ህዝቦች ልማት ማህበር የጀመረው የሰንበት ገቢያ በበዓል ወቅት ከሚፈጠረው የዋጋ ንረት ታድጎናል ሲሉ የሸካ ዞን ማሻ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።
More Stories
ሩሲያ ከመጋቢት 23 ጀምሮ የነዳጅ (ቤንዚን) ኤክስፖርት ልታግድ ነው።
የቡና ምርትን ለዓለም ገበያ በማቅረብ 43 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት ተችሏል፡- የኦሮሚያ ቡና አምራች ገበሬዎች ሕብረት ስራ ዩኒየን
በክልሉ የቡና አቅምን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር የሚያስችል ግዙፍ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት ጥያቄ እየቀረበ መሆኑ ተገለጸ።