ማሻ፤ መጋቢት 4/2018 ዓ/ም(ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) ማዕድን ሚኒስቴር በተለያዩ የማዕድን ምርት ለሚሰማሩ ሦስት ኩባንያዎች የምርት ፍቃድ ሰጥቷል፡፡
የማዕድን ሚኒስትር ሀብታሙ ተገኝ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፥ ኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፍ ያላትን ሀብት በተገቢው መንገድ ለማልማት ወሳኝ ርምጃዎችን እየወሰደች ትገኛለች፡፡
ለኩባንያዎቹ ፍቃድ መሰጠቱ ማዕድናቱን ወጥነት ባለው መልኩ ለማምረትና ወደ ውጭ ገበያ በማቅረብ የውጭ ምንዛሪን ለማስቀረት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው አብራርተዋል፡፡
በተጨማሪም ስትራቴጂያዊ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት የምርት ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ አቅም የሚፈጥር ነው ብለዋል።
ፍቃድ የተሰጣቸው ኩባንያዎች በፖታሽ፣ በብረትና በወርቅ ማዕድን ምርቶች የሚሰማሩ ሲሆን፥ ሦስቱም የማዕድን ምርቶች 2 ቢሊየን ዶላር ኢንቨስትመንት ወጪ የሚደረግባቸው መሆናቸው ተገልጿል፡፡
በዚህም መሰረት በፖታሽ ምርት ለኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ፣ በብረት ምርት ለዜድዋይቲ ቢዲአይኤም (ZYTBDIM) እንዲሁም በወርቅ ምርት ለቤሮ ማይኒንግ የማዕድን ምርት ፍቃድ ተሰጥቷል፡፡
(ኤፍ ኤም ሲ)
More Stories
በክልሉ ከሚገኙ ቡና አቅራቢ ነጋዴዎች ጋር በወቅታዊ የቡና ገበያ ላይ በቦንጋ ከተማ ምክክር እየተደረገ ነዉ
የጣሊያን ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያላቸውን የኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲያጠናከሩ ተጠየቀ፡፡
የዓለም የቡና ዋጋ በመቀነሱ አቅራቢዎች በእጃቸው ያለውን ምርት በፍጥነት ለገበያ እንዲያቀርቡ ጥሪ ቀረበ