ማሻ፤ መጋቢት 4/2018 ዓ/ም(ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) የአሜሪካ ነዳጅ ጫኝ የጦር አውሮፕላን በምዕራባዊ ኢራቅ መከስከሱ ተሰምቷል፡፡
የአሜሪካ ጦር ዲፓርትመንት እየበረሩ ላሉ ተዋጊ ጀቶች አየር ላይ ነዳጅ የሚሞላው “ኬሲ-135” አውሮፕላን መውደቁን በማረጋገጥ÷ አደጋው የተከሰተው በጠላት ወይም በወዳጅ ሀገር ተኩስ አይደለም ብሏል።
አደጋው ሁለት አውሮፕላኖች ላይ መከሰቱን ጠቅሶ÷ ነዳጅ መሙያ አውሮፕላኑ ሲከሰከስ ሌላኛው በሰላም መሬት ላይ ማረፉን ገልጿል፡፡
አውሮፕላኑ በተከሰከሰበት ምዕራባዊ ኢራቅ ውስጥ የነፍስ አድን ስራ እየተከናወነ መሆኑንም አመልክቷል።
አውሮፕላኑ ሲወቅድ በሰዎች ላይ ጉዳት ስለመድረሱ የተባለ ነገር የለም።
በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩ አምስት የአሜሪካ ወታደሮች በምን አይነት ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙም የታወቀ ነገር አለመኖሩን ቢቢሲ ዘግቧል።
የተከሰከሰው አውሮፕላን በጦርነቶች ውስጥ ከፍተኛ ሚና እንዳለውና ተዋጊ ጀቶች እና ቦንብ ጣይ አውሮፕላኖች ረጅም ርቀት ተጉዘው ዒላማዎችን በሚመቱበት ወቅት በቂ ነዳጅ እንዲኖራቸው እንደሚያደርግ ተገልጿል።
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።