ማሻ፤ የካቲት 17/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) ሁለቱ የለንደን ከተማ ክለቦች ቼልሲ እና ዌስትሃም ዩናይትድ ከእንግሊዝ እግርኳስ ማህበር የገንዘብ ቅጣት ተጥሎባቸዋል።
ክለቦቹ የገንዘብ ቅጣት የተጣለባቸው ብዛት ያላቸው ተጫዋቾች ሜዳ ውስጥ ለፀብ በመዳረጋቸው ነው።
ከሳምንታት በፊት ቼልሲ ከዌስሃም ዩናይትድ በተገናኙበት እና ቼልሲ ከ2ለ0 መመራት ተነስቶ 3ለ2 ባሸነፈበት ጨዋታ በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ላይ የሁለቱ ክለቦች ተጫዋቾች ፀብ ውስጥ መግባታቸው ይታወሳል።
ጉዳዩን ሲያጣራ የቆየው የእንግሊዝ እግርኳስ ማህበር ክለቦቹ ተጫዋቾቻቸውን መቆጣጠር ባለመቻላቸው የገንዘብ ቅጣት ጥሎባቸዋል።
በዚህም መሰረት የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ 325 ሺህ ፓውንድ ተቀጥቷል።
ዌስትሃም ዩናይትዶች ደግሞ የ300 ሺህ ፓውንድ የገንዘብ ቅጣት ተጥሎባቸዋል።
More Stories
አርሰናል እና ባየር ሙኒክ ለግማሽ ፍጻሜ ደረሱ
ፖርተኞች ፍፁም ስፖርታዊ ጨዋነት በመላበስ ውድድር ማካሄድ እንዳለባቸው የዉድድሩ ስነስርዓት ኮሚቴ ገለፀ።
አሜሪካዊቷ የኦሊምፒክ ሻምፒዮን አዲስ አበባ ገባች!