ማሻ፤ የካቲት 17/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) ሁለቱ የለንደን ከተማ ክለቦች ቼልሲ እና ዌስትሃም ዩናይትድ ከእንግሊዝ እግርኳስ ማህበር የገንዘብ ቅጣት ተጥሎባቸዋል።
ክለቦቹ የገንዘብ ቅጣት የተጣለባቸው ብዛት ያላቸው ተጫዋቾች ሜዳ ውስጥ ለፀብ በመዳረጋቸው ነው።
ከሳምንታት በፊት ቼልሲ ከዌስሃም ዩናይትድ በተገናኙበት እና ቼልሲ ከ2ለ0 መመራት ተነስቶ 3ለ2 ባሸነፈበት ጨዋታ በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ላይ የሁለቱ ክለቦች ተጫዋቾች ፀብ ውስጥ መግባታቸው ይታወሳል።
ጉዳዩን ሲያጣራ የቆየው የእንግሊዝ እግርኳስ ማህበር ክለቦቹ ተጫዋቾቻቸውን መቆጣጠር ባለመቻላቸው የገንዘብ ቅጣት ጥሎባቸዋል።
በዚህም መሰረት የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ 325 ሺህ ፓውንድ ተቀጥቷል።
ዌስትሃም ዩናይትዶች ደግሞ የ300 ሺህ ፓውንድ የገንዘብ ቅጣት ተጥሎባቸዋል።
More Stories
ሪያል ማድሪድ የዓለማችን ውዱ ክለብ ሆነ
ፒኤስጂ በተከታታይ ለ2ኛ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን አሸነፈ
ክሪስታል ፓላስ የአውሮፓ ኮንፍረንስ ሊግ ሻምፒዮን ሆነ!