ማሻ፤ ጥር 09/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) ብፁዕነታቸው ከከተራ እስከ ቃና ዘገሊላ ያለውን የጥምቀት በዓል ባማረና በደመቀ እንዲሁም ሀይማኖታዊ ትውፊቱን በጠበቀ መልኩ ለማክበር በሁሉም አካባቢዎች ዝግጅት መደረጉን ነው ያመላከቱት።
ጥምቀት ከጨለማ ወደብርሃን የተሻገርንበት፣እዳችን የተሰረዘበት፣ከወደቅንበት የተነሳንበትና የተጣላ የሚታረቅበት የድነት በዓል በመሆኑ በጉጉት የሚጠበቅ በዓል መሆኑንም አንስተዋል።
በዩኔስኮ ከማይዳሰሱ የአለም ቅርሶች አንዱ የሆነው ጥምቀት አብሮነትን የሚያጠናክር በመሆኑ ኢትዮጵያውያንን በአጠቃለይ የሚወክል ነው ብለዋል።
ታቦታቱ ከመንበራቸው ወጥተው ወደ ጥምቀተ ባህር የሚሄዱበት ሂደት ኢየሱስ ክርስቶስ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ለመጠመቅ የሄደበትን ማሳያ እንደሆነ ገልፀዋል።
በዓሉን የተቸገሩ ወገኖችን በመደገፍ ልናሳልፍ ይገባልም ነው ያሉት።
ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በአሉ የፍቅርና የአብሮነት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
#Southwestmedianetwork
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።