ማሻ፣ ጥር 06/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍኤም 103.8) በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዙሪያ በቱሪዝምና በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ለሚሰማሩ ባለሀብቶች መንግሥት የመሬት አቅርቦትን ጨምሮ ልዩ ልዩ ድጋፎችን እንደሚያደርግ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ስለሺ ግርማ ገለጹ።
ሚኒስትር ዴኤታው በጉባ በተካሄደው “ስለ ኢትዮጵያ” የውይይት መድረክ ላይ ተገኝተው እንደገለጹት፤ መንግሥት በሕዳሴ ግድቡ፣ በደሴቶችና በንጋት ሐይቅ አካባቢ ማልማት ለሚፈልጉ ባለሀብቶች የመሬት አቅርቦትን በሊዝ እና በተለያዩ አማራጮች ያመቻቻል።
በተጨማሪም ለኢንቨስትመንት ሥራው የሚሆን የፋይናንስ ብድር በባንኮች በኩል እንዲመቻች እንደሚደረግና ለግንባታ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ከውጭ ሲገቡ ከቀረጥ ነፃ እንዲሆኑ መወሰኑን ሚኒስትር ዴኤታው አስታውቀዋል።
በሪዞርቶች፣ በሎጅዎችና በሌሎች የቢዝነስ አማራጮች ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሠራተኛ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎችን ለማስገባት መንግሥት ድጋፍ እንደሚያደርግም ጠቁመዋል።
የሰው ኃይል እጥረትን ለመቅረፍ በቁልፍ የአመራር ቦታዎች ላይ የውጭ ባለሙያዎችን ለማምጣት እንደሚፈቀድ የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ባለሀብቶች በሆቴል፣ በሬስቶራንት፣ በውኃ ትራንስፖርትና በኩነት ዝግጅት ዘርፎች እንዲሰማሩ ጥሪ አቅርበዋል።
ይህ ማበረታቻ በግድቡ ዙሪያ የሚገነቡ የቱሪዝም መዳረሻዎችን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ለማድረግ ያለመ መሆኑን አብራርተዋል።
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች