ማሻ፣ ታህሳስ 27/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍኤም 103.8) በዓሉን ምክንያት በማድረግ ሊከሰት የሚችል ማንኛውም ችግርና ድንገተኛ አደጋ ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ ክስተቶችን መከላከል በሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ በቂ ዝግጅት መደረጉን መምሪያው ገልጿል ።
በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት ከሚከበሩ በዓላት መካከል አንዱ የሆነው የገና በዓል በሰላም ተከብሮ እንዲያልፍ በየደረጃው ከሚገኙ የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን በቂ ዝግጅት መደረጉን የሸካ ዞን ፓሊስ አዛዥ ምክትል ኮማንደር አስታውሰኝ አይሞ ተናግረዋል ።
በዓሉን ምክንያት በማድረግ ሊከሰቱ የሚችሉ ዝርፊያ ፣ ንጥቂያና ሌሎች የማጭበርበር ወንጀሎችን ቀድሞ መከላከል በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ትኩረት መደረጉን ምክትል ኮማንደሩ ገልፀዋል ።
በበዓል ሰሞን የትራፊክ አደጋ እንዳይከሰት የትራፊክ ፖሊስ ከሚያደርገው ቁጥጥርና ክትትል በተጨማሪ አሽከርካሪዎች በጥንቃቄ እንዲያሽከረክሩ አሳስበዋል።
ከበዓል ስራዎች ጋር ተያይዞም የእሳት አደጋ ሊፈጠር የሚችል በመሆኑ በተለይ በቤት ውስጥ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግም ጭምር ተናግረዋል ።
በበዓል ወቅት ለጸጥታ ስጋት የሆኑ እንቅስቃሴዎች ሲያጋጥሙ ህብረተሰቡ ለጸጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠት የድርሻቸውን እንዲወጣ ያሳሰቡት ምክትል ኮማንደር አስታውሰኝ በዓሉ የሰላም ፣የደስታና የፍቅር እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል ።
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።