ማሻ፣ ታህሳስ 19/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) የማርበርግ ቫይረስ ስጋት ባለባቸው አካባቢዎች የሕይወት አድን መድኃኒቶችንና ክትባቶችን በድሮን የማድረስ ሥራ ዛሬ በይፋ ተጀምሯል።
የጤና ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በመተባበር ነው በድሮን የታገዘውን የክትባት ሥርጭት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዳሰነች ወረዳ ያስጀመሩት፡፡
መርሐ ግብሩ ሚኒስቴሩ የወረርሽኙን ሥርጭት ለመግታትና ራቅ ያሉ አካባቢዎች የሚገኙ ዜጎችን ሕይወት ለመታደግ የወሰደው ፈጣን ምላሽ ርምጃ አካል ነው፡፡
በዚህ መሰረትም በዛሬው ዕለት በዳሰነች ወረዳ በድሮን የታገዘ የክትባት ሥርጭት በስኬት መከናወኑን ጤና ሚኒስቴር ለፋና ዲጂታል ገልጿል፡፡
የዳሰነች ወረዳ ካለው ራቅ ያለ መልክዓ ምድር አኳያ በመኪና ለማጓጓዝ ረጅም ሰዓታት ይወስድ የነበረውን ጉዞ በድሮን በመታገዝ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ክትባቱን ማዳረስ መቻሉ ተመላክቷል፡፡
ይህም ጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅርቦት አገልግሎት የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በመጠቀም ወረርሽኞችን ቀድሞ የመከላከልና የመቆጣጠር አቅማቸውን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገራቸውን በተግባር ያሳዩበት ነው።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ ወረርሽኞችን ለመመከት የራሷን የውስጥ አቅም እና የቴክኖሎጂ ውጤቶች መጠቀም መጀመሯን የሚያሳይ ትልቅ ተግባር መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች