ማሻ፣ ታህሳስ 17/2018 (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የደቡብ ምዕራብ ሪጅን በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ ከባለድርሻ አካላትና ከቁልፍ ደንበኞች ጋር ውጤታማ የምክክር መድረክ አከናውኗል።
ተሳታፊዎች ተደጋጋሚ የኃይል መቆራረጥ እንዲቆም፣ ያረጁ የእንጨት ምሶሶዎች በኮንክሪት እንዲቀየሩ፣ የሰብስቴሽን እጥረት እንዲፈታና የአገልግሎት ክፍያ እንዲቀነስ ጠይቀዋል።
የሪጅኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ገብሬ በሰጡት ምላሽ፤ የመስመር ዝርጋታና የኮንክሪት ፖል ጥያቄዎችን ለመፍታት ዕቅድ መያዙን ገልጸዋል። የኃይል ተደራሽነትን ለማስፋትም ከጊቢ የኃይል ማመንጫ ለማምጣት ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
ውይይቱ የተቋሙን ተጠያቂነት ለማስፈንና የፕሮጀክቶችን ስኬት ለመጨመር ያለመ ሲሆን፤ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ደንበኞችም የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።
ተቋሙ በተመጣጣኝ ዋጋ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብና የአገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን ቁርጠኛ መሆኑን በድጋሚ አረጋግጧል። ዘገባው የደ.ምዕ. ሚዲያ ኔትዎርክ ነው።
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።