February 4, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ብጹዕ አቡነ ሕዝቅኤል በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

ማሻ፣ ታህሳስ 17/2018 (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) ብጹዕ አቡነ ሕዝቅኤል የከፋ ሸካ ቤንች ሸኮ እና ምዕራብ ኦሞ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ:የሰዋስው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ጠባቂ እና የሲኖዶስ አባል በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው ።

ብጹዕነታቸው በቆይታቸውም የሸካ ሀገረ ስብከትን በማቋቋም ለሀገረ ስብከት ጽ/ቤት እና መንበረ ጵጵስና ግንባታ መሠረተ ድንጋይ እንደሚያስቀሚጡ የሚጠበቅ ነው ።

ብጹዕ አቡነ ሕዝቅኤል የከፋ ሸካ ቤንች ሸኮ እና ምዕራብ ኦሞ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ:የሰዋስው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ጠባቂ እና የሲኖዶስ አባልን ጨምሮ የሀገረ ስብከቱ ልዑክ ጋር  በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል ።

በአቀባበል ስነ ስረዓቱ ላይ የየኪ ወረዳ ቤተኪህነት ፣ የአራቱ አድባራት አገልጋዮች ፣ ማህበረ ቅዱሳን የቴፒ ወረዳ ማዕከል፣ የማሻና የጌጫ አጥቢያ ቤተክርስቲያናት አገልጋዮችና የሰበካ ጉባኤ አባላትን ጨምሮ ሌሎች የሃይማኖት አባቶችና የእምነቱ ተከታዮች ታድመዋል ።