ማሻ፣ ታህሳስ 17/2018 (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) ብጹዕ አቡነ ሕዝቅኤል የከፋ ሸካ ቤንች ሸኮ እና ምዕራብ ኦሞ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ:የሰዋስው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ጠባቂ እና የሲኖዶስ አባል በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው ።
ብጹዕነታቸው በቆይታቸውም የሸካ ሀገረ ስብከትን በማቋቋም ለሀገረ ስብከት ጽ/ቤት እና መንበረ ጵጵስና ግንባታ መሠረተ ድንጋይ እንደሚያስቀሚጡ የሚጠበቅ ነው ።
ብጹዕ አቡነ ሕዝቅኤል የከፋ ሸካ ቤንች ሸኮ እና ምዕራብ ኦሞ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ:የሰዋስው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ጠባቂ እና የሲኖዶስ አባልን ጨምሮ የሀገረ ስብከቱ ልዑክ ጋር በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል ።
በአቀባበል ስነ ስረዓቱ ላይ የየኪ ወረዳ ቤተኪህነት ፣ የአራቱ አድባራት አገልጋዮች ፣ ማህበረ ቅዱሳን የቴፒ ወረዳ ማዕከል፣ የማሻና የጌጫ አጥቢያ ቤተክርስቲያናት አገልጋዮችና የሰበካ ጉባኤ አባላትን ጨምሮ ሌሎች የሃይማኖት አባቶችና የእምነቱ ተከታዮች ታድመዋል ።
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።