አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ቡርኪና ፋሶ ኢኳቶሪያል ጊኒን 2 ለ 1 አሸንፋለች።
ቀን 9:30 ላይ በተካሄደው ጨዋታ ቡርኪና ፋሶ በጭማሪ ደቂቃ ላይ ኤድመንድ ታፕሶባ እና ጆርጂ ሚኖንጎ ባስቆጠሯቸው ግቦች ሶስት ነጥብ ይዛ ወጥታለች።
ባሲሊዮ ንዶንግ በሰራው ጥፋት በቀይ ካርድ የተሰናበተባት ኢኳቶሪያል ጊኒ ማርቪን አኒየቦህ ባስቆጠራት ግብ እየመራች ቆይታ ባለቀ ሰዓት በተቆጠረባት ግብ አሳዛኝ ተሸናፊ ሆናለች።
More Stories
ማንቼስተር ዩናይትድ በአስቶን ቪላ ተሸነፈ
በአፍሪካ ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ አንጎላን አሸነፈች
አንድሬ ኦናና ከቅድመ ውድድር ዘመን ጨዋታዎች ውጪ ሆነ