የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም እንደገለፁት በአገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጠዉን የልጅነት ልምሻ በሽታ መከላከያ ክትባት በክልላችን ዉጤታማ ለማድረግ የቅድመ ዝግት ስራዎች ሲሰሩ እንደቆዩና በዘመቻዉም 564 ሺህ 624 እድሚያቸዉ ከ5አመት በታች የሚሆኑ ልጆች ተደራሽ እንደሚደረጉ ገልጸዋል::
የቢሮ ኃላፊ እንደገለጸት በ1ኛዉ ዙር ዘመቻ ከታቀደዉ እቅድ 100% በላይ ክትባቱን ተደራሽ ማድረግ የተቻለ ሲሆን በ2ኛዉ ዙርም 1ኛ ዙር የወሰዱ ልጆች ተደረሽ ለማድረግ የቅድመ ዝግጅት በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን ጠቅሰዉ ሁሉንም ታላሚዎች ተደራሸ ለማድረግ በየደረጃዉ የሚገኙትን ባለድርሻ አካላት ባሰተፈ መልኩ ዘመቻዉ መመራት እንዳለበት አሳስበዋል::
የቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም እንደገለጸት በዘመቻዉ ወቅት ተቀናጅተዉ የሚሰሩ ተግባራት ኤም ፖክስ (M_Pox) በሽታ ግንዛቤ የመፍጠር እና የአሰሳ ስራ፥ በኩፍኝ ክትባት ዘመቻ ወቅት የተለዩ የተወሳሰበ የስርዓተ ምግብ ችግር ያለባቸዉን ልጆች ወደ ጤና ተቋም ሄደዉ ህክምና እንዲጀምሩ አሳስበዋል።
እድሜያቸው ከ1አመት በላይ ሆነዉ ክትባት ያልጀመሩና ጀምረዉ ያቋረጡ ልጆች ክትባት እንዲጀምሩ ማድረግ፤ቆልማማ እግር ችግር ያለባቸዉን ልጆች ልየታ፤የፊስቱላ ልየታ ስራዎች የሚሰሩ ሲሆን በዘመቻዉ ላይ የተሰማሩ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ተግባራትን በትኩረት እንዲተገብሩና እንዲመሩ ጥሪ አቅርበዋል።
በመቀጠልም ዘመቻዉን በተቀመጠዉ የጊዜ ሰሌዳ ለማድረግ ይረዳ ዘንድ በየደረጃዉ የሚገኙ ባለድርሻ አካላት የተለመደዉን ትብብር እንዲያደርጉ የቢሮ ኃላፊ አሳስበዋል::
More Stories
ከ90 በላይ ኩባንያዎች የሚሳተፉበት ዓለም አቀፍ አውደርዕይ ሊካሄድ ነው
ኤች አይ ቪ ኤድስን በመከላከልና በመቆጣጠር በዜጎች ማህበራዊ ሕይወት ላይ ተጽእኖ እንዳያሳድር በማድረግ ክልላዊና ሀገራዊ ግቦችን ማሳካት እንደሚገባ ተገለፀ ።
ሕፃናት ወደ አፋቸው የሚያስገቧቸው ባዕድ ነገሮች እስከ ሞት ለሚያደርስ አደጋ እያጋለጣቸው ነው፦ የሕፃናት ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት