ማሻ ፣ የግንቦት 05፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም)በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ 2025 ፎረም ላይ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከ1 ነጥብ 6 ቢሊየን ዶላር በላይ የኢንቨስትመንት ስምምነቶችን ተፈራረመ፡፡
ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ 2025 ፎረም ዛሬ ተጠናቅቋል፡፡
በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት ለኢንቨስትመንት በቁርጠኝት እየሠራ መሆኑ በስፋት መነሳቱ ተገልጿል።
ኢትዮጵያ በግብርናና አግሮፕሮሰሲንግ፣ በማምረቻ፣ በአገልግሎት፣ በአይሲቲ እና በሌሎችም ዘርፎች ከፍተኛ አቅም እንዳላት ያሳየችበት መድረክ መሆኑን የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) አስታውቀዋል፡፡
በሀገሪቱ የተወሰዱ የኢኮኖሚ ሪፎርሞችም ለኢንቨስትመንት ዘርፉ ወሳኝነት ያላቸው መሆኑን አብራርተዋል።
ፋና
More Stories
በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ የአቮካዶ ምርቶች ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ገበያ ተፈላጊ እያደረጓት ነው
ከወጪ ንግድ 607 ሚሊየን ዶላር ገቢ ተገኘ
በጅማ ዞን የተመረተ ከ6.7 ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ የአቮካዶ እና የሙዝ ምርት ለገበያ ቀረበ