ማሻ ፣ የግንቦት 04፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) መምሪያው የኩፍኝ መከላከያ ክትባት ዘመቻን ለማሰጀመር ዓላማ ያደረገ የንቅናቄ መድረክ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በቴፒ ከተማ አካሂዷል ።
የሸካ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ እምሩ ወዬሳ በዚህ ወቅት እንደተናገሩት የክትባት ዘመቻው ውጤታማ እንድሆን ለዘርፍ ባለሙያዎች ስልጠና ከመስጠት በተጨማሪ አስፈላጊ የሆኑ ግባቶችን የሟሟላት ስራ ተሰርቷል ብለዋል።
ከዘመቻው ጎን ለጎን ህብረተሰቡ ጤናውን እንድጠብቅ የግንዛቤ ስራዎች እንደምሰራ የገለፁት ኃላፊው የክትባት ዘመቻው እንዲሳካ የተሽከርካሪና ሌሎች ድጋፎችን እንደምጠይቅ ገልፀዋል ።
የሸካ ዞን አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊና የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ምንተስኖት እንዳሻው በበኩላቸው የዚህ ክትባት ዘመቻ ዕቅድ እንድሳካ በየደረጃው የምገኙ ባለድርሻ አካላት ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል ።
ለዚህም የዞን አስተዳደር የበኩሉን ድጋፍ እንደምያደርግ ጠቁመው በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች፤ ባለሙያዎች እንድሁም የሀይማኖት አባቶች እና የማህበረሰብ ክፍሎች የበኩላቸውን እንድወጡ አሳስበዋል ።
በዞኑ ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ 48 ሺህ 3መቶ 38 ህጻናት በጤና ተቋማትና ጊዜያዊ የክትባት መስጫ ጣቢያዎች የሚሰጥ ሲሆን የሀይማኖት አባቶችና ለሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ዘመቻው እንዲሳካ አስፈለጊውን ድጋፍ እንድያደርጉ ጥር ቀርቧል።
የመከላከያ ክትባት ዘመቻው ከግንቦት 6 እስከ 15 ቀን 2017 ዓ/ም ድረስ ለተከታታይ 10 ቀናት እንደሚሰጥም ተገልጿል።
ዘጋቢ አስቻለው አየለ
More Stories
ከ 315 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎ የምጠበቀው የTELCOM+ የተቀናጀ የጤና ዘመቻ በሸካ ዞን የኪ ወረዳ ፊዴ ቀበሌ በይፋ ተጀመረ
በ8 ክልሎች ከ41 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ሀገር አቀፍ የተቀናጀ የጤና ምርመራ ዘመቻ ተጀመረ
ዘመቻው ስኬታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት ተጠናቅቋል፦ የክልሉ ጤና ቢሮ