ማሻ ፣ የመጋቢት 29፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የፓስፖርት አገልግሎት ደንበኞችን በማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ ሁለት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አስታውቋል፡፡
ከአገልግሎቱ የተገኘው መረጃ እንዳመለከተው ተጠርጣሪዎቹ አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን የሚል ማታለያ በመጠቀም በ24 የአገልግሎቱ ደንበኞች ላይ የማጭበርበር ወንጀል መፈጸማቸው ተጠቅሷል፡፡
የወንጀል ድርጊቱን ፈፅመዋል የተባሉት ተጠርጣሪዎች ተቋሙ ለ5 ቀን 20 ሺህ ብር የሚያስከፍለውን 28 ሺህ ብር ሲያስከፍሉ መቆየታቸውም ነው የተገለፀው፡፡
አገልግሎቱ ከፌደራል ፓሊስ እና ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በቅንጅት ባደረገው ክትትል ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ውለው፣ ተገልጋዮቹ የከፈሉት ገንዘብ እንዲመለስ መደረጉ ተመላክቷል፡፡
ደንበኞች ከመሰል የማጭበርበር ተግባር ራሳቸውን እንዲጠብቁ እንዲሁም ስለአገልግሎቱ ማንኛውም አይነት መረጃ ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የመረጃ ዴስክ አልያም ከተቋሙ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እንዲያገኙ አገልግሎቱ አሳስቧል፡፡
ኢቢሲ
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።