ማሻ ፣ የመጋቢት 29፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የፓስፖርት አገልግሎት ደንበኞችን በማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ ሁለት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አስታውቋል፡፡
ከአገልግሎቱ የተገኘው መረጃ እንዳመለከተው ተጠርጣሪዎቹ አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን የሚል ማታለያ በመጠቀም በ24 የአገልግሎቱ ደንበኞች ላይ የማጭበርበር ወንጀል መፈጸማቸው ተጠቅሷል፡፡
የወንጀል ድርጊቱን ፈፅመዋል የተባሉት ተጠርጣሪዎች ተቋሙ ለ5 ቀን 20 ሺህ ብር የሚያስከፍለውን 28 ሺህ ብር ሲያስከፍሉ መቆየታቸውም ነው የተገለፀው፡፡
አገልግሎቱ ከፌደራል ፓሊስ እና ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በቅንጅት ባደረገው ክትትል ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ውለው፣ ተገልጋዮቹ የከፈሉት ገንዘብ እንዲመለስ መደረጉ ተመላክቷል፡፡
ደንበኞች ከመሰል የማጭበርበር ተግባር ራሳቸውን እንዲጠብቁ እንዲሁም ስለአገልግሎቱ ማንኛውም አይነት መረጃ ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የመረጃ ዴስክ አልያም ከተቋሙ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እንዲያገኙ አገልግሎቱ አሳስቧል፡፡
ኢቢሲ
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።