ማሻ ፣ የመጋቢት 24፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ትናንት ፤ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና በሚል መርህ ቃል ባለፋት የለውጥ አመታት በየዘርፉ የተከናወኑ ተግባራትን የሚገምግም እና የለውጡን ትሩፋቶች የሚዘክር መድረክ በቦንጋ ከተማ ተጀምሯል ።
የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪው መድረኩን ሲከፍቱ መጋቢት 24 ኢትዮጵያን የሚያሻግሩ መሰረቶች የተጣሉበት በመሆኑ ሁሌም ይዘከራል ብለዋል ።
ባለፉት የለውጥ አመታት የህዝቡን የጋራ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራት በየዘርፉ መከናወናቸውንም የመንግስት ዋና ተጠሪው አውስተዋል መላው አመራርና ህዝቡ የለውጡ ትሩፋቶችን ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የተጀመረውን ርብርብ እንዲያጠናክረው ጥሪ አቅርበዋል ።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር እና የብልፅግና ፓርቲ ስራአስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አቶ ማስረሻ በላቸው በበኩላቸው የለውጡ መንግስት በየዘርፉ የቀየሳቸው አቅጣጫዎች የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቁመዋል ።
ከተረጂነት ለመላቀቅ በተደረገው ርብርብ የግብርና ምርታማነት ማደጉን በመጥቀስ።
በሰላም፣ብዝሃነት እና አብሮነት ዕሴቶች ግንባታ ዘርፍ በተከናወኑ ተግባራት ወንድማማችነትንና ትብብርን የሚያስቀድም የፖለቲካ ስርዓት መገንባት መቻሉን አቶ ማስረሻ ጠቁመዋል ።
መጋቢት 24ን ማስታወስ ባለፉት 7 አመታት የተከናወኑ ተግባራትንና የተመዘገቡ ድሎችን ለማስቀጠል የሚያስችል መነሳሳት እንደሚፈጥር የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር እና የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አቶ ማስረሻ በላቸው አስገንዝበዋል።
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።