ማሻ፣ መጋቢት 8፣ 2017 (ደሬተድ ማሻ ቅርንጫፍ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ የተረከበው ቦይንግ 737-800 የተሰኘ የቢዝነስ ጀት አውሮፕላን ልዩ አገልግሎት ለሚሹ ደንበኞቹ እንደሚውል ተጠቁሟል።
ከዚህ ቀደም ለልዩ በረራዎች የሚውሉ አገልግሎቶችን በመደበኛ አውሮፕላኖች ሲሰጥ መቆየቱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው ተናግረዋል።
አዲሱ አውሮፕላን ዘመናዊ አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ውስጣዊ ክፍሎች እንዳሉት ገልጸው፤ በመደበኛ አገልግሎት ላይ ይፈጥር የነበረውን ጫና እንደሚቀንስ ጠቁመዋል።
አየር መንገዱ በቻርተር አውሮፕላን አገልግሎት አሰጣጥ ላይ አቅሙን ለማሳደግ መሰል አውሮፕላኖች እንደሚያግዙት ተናግረዋል።
አየር መንገዱ በ2035 የአገልግሎት አድማሱን ለማስፋት የያዘውን ውጥን ለማሳካት መሰል ተጨማሪ የቢዝነስ አውሮፕላኖችን ወደ ስራ እንደሚስገባ ተገልጿል።
ኤፍ ኤም ሲ
More Stories
ግብርናን ዘርፍ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር የፋይናንስ ብድር አገልግሎት
በሸካ ዞን አንድራቻ ወረዳ እየተከናወኑ የሚገኙ የተቀናጁ የልማት ሥራዎች በክልልና በዞን ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ አባላት ምልከታ ተደረገ
ቆጮን ኬክና ኩኪስ አድርገን ባህር ማዶ አሻግረናል – ሉሲ የእንሰት ኢንተርፕራይዝ