ማሻ፣ መጋቢት 2፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) ማንቼስተር ዩናይትድ 100 ሺህ ተመልካቾችን የሚያስተናግድ አዲስ ግዙፍ ስታዲየም ሊገነባ መሆኑን ይፋ አድርጓል፡፡
በሁለት ቢሊየን ፓውንድ ወጪ የሚገነባው አዲሱ ስታዲየም በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃልም ነው የተባለው፡፡
ክለቡ ለ115 ዓመታት ያህል ሲገለገልበት ከቆየው ኦልድትራፎርድ አቅራቢያ የሚገነባው አዲሱ ስታዲየም እስከሚጠናቀቅ ድረስ በዛው በኦልድትራፎርድ ጨዋታዎቹን እንደሚያከናውን ተገልጿል፡፡
ክለቡ ይፋ ባደረገው ዲዛይን መሰረት ስታዲየሙ እያንዳንዳቸው 200 ሜትር ከፍታ ያላቸው ሶስት ምሶሶዎች እንደሚኖሩትም የቢቢሲ ስፖርት ዘገባ አመላክቷል፡፡
ኤፍ ኤም ሲ
የአዲሱ ስታዲየም ፕሮጀክት ይፋ ከመደረጉ በፊት ነባሩን ኦልድትራፎርድ ማደስ አልያም አዲስ ስታዲየም መገንባት በሚለው ጉዳይ ላይ ሰፊ ውይይት ሲደረግ መቆየቱንም ዘገባው አስታውሷል፡፡
More Stories
የሸካ ዞን የታዳጊ ወጣቶች የእግርኳስ ቡድን የ2018 ክልል አቀፍ ውድድር የዋንጫ አሸናፊ ሆነ።
5ተኛው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር፣ የባህል ፌስቲቫል እና የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የታለመውን ግብ ያሳካ መሆኑ ተገለጸ።
ባካሪ ሳኛ ኢትዮጵያ ገባ