ማሻ፣ ጥር 29፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) ብራዚላዊው የቀድሞው የሪያል ማድሪድ ተከላካይ ማርሴሎ ከእግር ኳስ ራሱን ማግለሉን አስታወቀ፡፡
የግራ መስመር ተከላካዩ ማርሴሎ በሪያል ማድሪድ ቤት ስኬታማ ጊዜን ያሳለፈ ሲሆን 5 የሻምፒዮንስ ሊግ እና 6 የላሊጋ ዋንጫዎችን ከሎስ ብላንኮቹ ጋር ማንሳት ችሏል፡፡
ለብራዚል ብሔራዊ ቡድን ደግሞ 58 ጊዜ ተሰልፎ በመጫዎት 6 ጎሎችን በስሙ አስመዝግቧል፡፡
ከሪያል ማድሪድ በመውጣት በግሪኩ ኦሎምፒኮስ እና በብራዚሉ ፉለሉሜንሴ ያልተሳካ ጊዜያት ያሳለፈው ማርሴሎ ከደቂቃዎች በፊት በለቀቀው ተንቀሳቃሽ ምስል በይፋ ጫማ መስቀሉን አስታውቋል፡፡
(ኤፍ ኤም ሲ)
More Stories
የሸካ ዞን የታዳጊ ወጣቶች የእግርኳስ ቡድን የ2018 ክልል አቀፍ ውድድር የዋንጫ አሸናፊ ሆነ።
5ተኛው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር፣ የባህል ፌስቲቫል እና የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የታለመውን ግብ ያሳካ መሆኑ ተገለጸ።
ባካሪ ሳኛ ኢትዮጵያ ገባ