ማሻ፣ የካቲት 12፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ምሽት አስቶን ቪላ ከሊቨርፑል የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
ምሽት 4፡30 በሚካሄደው ጨዋታ አስቶን ቪላ በሜዳው ሊጉን በመምራት ላይ የሚገኘውን ሊቨርፑል የሚገጥም ይሆናል፡፡
በጥሩ የዝውውር መስኮት ንቁ ተሳታፊ የነበሩት እና ጠንካራ ተጫዋቾችን ያስፈረሙት ቪላዎቹ የሊጉን ዋንጫ ለማንሳት እየተፋለመ ለሚገኘው ሊቨርፑል ፈተና እንደሚሆኑበት ይጠበቃል።
በጨዋታው ከሊቨርፑል በኩል ኮዲ ጋክፖ እና ጆ ጎሜዝ በጉዳት ምክንያት እንደማይሰለፉ ተመላክቷል፡፡
More Stories
ትዕግስት አሰፋ በዓለም አቀፉ የድንቃ ድንቅ መዝገብ እውቅና ተሰጣት
ኢትዮጵያ በፊፋ ደረጃ 147ኛ ሆናለች
ኬቨን ዲብሮይን በውድድር ዓመቱ መጨረሻ ማንቼስተር ሲቲን እንደሚለቅ ተረጋገጠ