ማሻ፣ የካቲት 12፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ምሽት አስቶን ቪላ ከሊቨርፑል የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
ምሽት 4፡30 በሚካሄደው ጨዋታ አስቶን ቪላ በሜዳው ሊጉን በመምራት ላይ የሚገኘውን ሊቨርፑል የሚገጥም ይሆናል፡፡
በጥሩ የዝውውር መስኮት ንቁ ተሳታፊ የነበሩት እና ጠንካራ ተጫዋቾችን ያስፈረሙት ቪላዎቹ የሊጉን ዋንጫ ለማንሳት እየተፋለመ ለሚገኘው ሊቨርፑል ፈተና እንደሚሆኑበት ይጠበቃል።
በጨዋታው ከሊቨርፑል በኩል ኮዲ ጋክፖ እና ጆ ጎሜዝ በጉዳት ምክንያት እንደማይሰለፉ ተመላክቷል፡፡
More Stories
የሸካ ዞን የታዳጊ ወጣቶች የእግርኳስ ቡድን የ2018 ክልል አቀፍ ውድድር የዋንጫ አሸናፊ ሆነ።
5ተኛው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር፣ የባህል ፌስቲቫል እና የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የታለመውን ግብ ያሳካ መሆኑ ተገለጸ።
ባካሪ ሳኛ ኢትዮጵያ ገባ