በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን “ለዓመታት ተንሰራፍቶ የነበረው” የሰራተኞች የውስጥ ችግር በውይይት መፈታቱ ተገልጿል፡፡
አለመግባባቱ የተፈታው የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት እና የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ከሠራተኞች ጋር ባደረጉት “ግልፅ” ውይይት መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
ፌዴሬሽኑ ጉዳዩን አስመልክቶ በማኀበራዊ ትስስር ገጹ ባስተላለፈው መልዕክት ፤ ፌዴሬሽኑ “ለዓመታት ተከማችቶ የነበረውን የሠራተኞች አለመግባባት ችግር በውይይት ሙሉ በሙሉ በመፍታት ደማቅ ታሪክ ፅፏል” ብሏል፡፡
በመድረኩ በየሥራ ሂደቱ የተከናወኑ ተግባራት ተገምግመው የ100 ቀናት የሥራ ዕቅድ ላይ ውይይት መደረጉም ተመላክቷል፡፡
More Stories
የሸካ ዞን የታዳጊ ወጣቶች የእግርኳስ ቡድን የ2018 ክልል አቀፍ ውድድር የዋንጫ አሸናፊ ሆነ።
5ተኛው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር፣ የባህል ፌስቲቫል እና የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የታለመውን ግብ ያሳካ መሆኑ ተገለጸ።
ባካሪ ሳኛ ኢትዮጵያ ገባ