በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን “ለዓመታት ተንሰራፍቶ የነበረው” የሰራተኞች የውስጥ ችግር በውይይት መፈታቱ ተገልጿል፡፡
አለመግባባቱ የተፈታው የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት እና የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ከሠራተኞች ጋር ባደረጉት “ግልፅ” ውይይት መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
ፌዴሬሽኑ ጉዳዩን አስመልክቶ በማኀበራዊ ትስስር ገጹ ባስተላለፈው መልዕክት ፤ ፌዴሬሽኑ “ለዓመታት ተከማችቶ የነበረውን የሠራተኞች አለመግባባት ችግር በውይይት ሙሉ በሙሉ በመፍታት ደማቅ ታሪክ ፅፏል” ብሏል፡፡
በመድረኩ በየሥራ ሂደቱ የተከናወኑ ተግባራት ተገምግመው የ100 ቀናት የሥራ ዕቅድ ላይ ውይይት መደረጉም ተመላክቷል፡፡
More Stories
አርሰናል ከ20 ዓመት በኋላ በሻምፒዮንስ ሊግ ለፍጻሜ ደረሰ
ማንቼስተር ዩናይትድ ሊቨርፑልን በማሸነፍ የሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎውን አረጋገጠ
ኬንያዊው አትሌት በሽልማት ተንበሸበሸ