ዮርዳኖስ ከዌስትባንክ ጋር በሚያዋስናት የድንበር መተላለፊያ የተፈጸመውን ጥቃት እየመረመርኩ ነው ብላለች
ሶስት እስራኤላውያን በዮርዳኖስ እና ዌስትባንክ መተላለፊያ ድንበር ተተኩሶባቸው ተገደሉ።
እያሽከረከረ ከወደ ዮርዳኖስ ወደ ዌስትባንክ የገባው ግለሰብም በጸጥታ ሃይሎች መገደሉን የእስራኤል ባለስልጣናት ተናግረዋል።
ህይወታቸው ያለፈው እስራኤላውያን እድሜያቸው ከ50 አመት በላይ የሆነ ወንዶች መሆናቸውን የእስራኤል አስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት ተቋም ገልጿል።
ዮርዳኖስ “አለንቢ” በተሰኘው መተላለፊያ የተፈጸመውን ግድያ እየመረመርኩ ነው ማለቷን የሀገሪቱ ብሄራዊ የዜና ወኪል ፔትራ ኒውስ አስነብቧል።
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ግድያውን አጥብቀው ያወገዙት ሲሆን፥ ከኢራን እና ከምታስታጥቃቸው ሃይሎች ጋር የሚገናኝ ጥቃት ነው ብለዋል።
Al-Ain
More Stories
አሜሪካ በኢራን ላይ የአየር ጥቃት ፈፀመች
አሜሪካ በኢራን ላይ አዲስ የአየር ጥቃት ፈፀመች
በ24 ሰዓት ውስጥ 25 መርከቦች በሆርሙዝ ሰርጥ አልፈዋል – ኢራን