የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በሐረር ከተማ የምስራቅ ዕዝን የ47 ዓመታት ጉዞ የሚዘክረውን ሙዚዬም ጎብኝተዋል፡፡በ1979 ዓ.ም የተቋቋመ የምስራቅ ዕዝ ሙዚዬም ለረጅም ዓመታት ከአገልግሎት ውጪ ሆኖ የቆየና በዕዙ ድጋፍ ለጉብኝት ክፍት የተደረገ መሆኑ ተገልጿል።በጉብኝቱ በሶማሊያ ወረራ ወቅት የኢትዮጵያ ዳር ድንበር ለማስጠበቅ የምስራቅ ዕዝ የተጠቀማቸው ተዋጊ አውሮፕላኖች፣ ቀላልና ከባድ የጦር መሳሪያዎች ለዕይታ ቀርበዋል፡፡ከሶማሊያ ጦር የተማረኩ ብረት ለበስ ተሽከርካሪዎች፣ ታንኮች ፣ የሙዚቃና የስፖርት ትጥቆችን ጨምሮ የዕዙን የ47 ዓመታ ታሪክ የሚገልፁ ቅርሶች መጎበኝታቸውንም የመከላከያ ሰራዊት ማህበራዊ ትስስር ገጽ መረጃ ያመላክታል፡፡በጉብኝቱ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ ም/ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጀኔራል አበባው ታደሰና ጀኔራል ጌታቸው ጉዲናን ጨምሮ ከፍተኛ የሰራዊቱ አመራሮችና የሃይማኖት አባቶች ተሳትፈዋል።
FBC
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።