ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቤይጂንግ ቆይታቸው ከቻይና ኮሙኒኬሽን እና ኮንስትራክሽን ኩባንያ (ሲሲሲሲ) ጋር ከጥቂት ወራት በፊት የተጀመረውን ውይይት ዛሬ ቀጥለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሲሲሲሲ የኢትዮጵያን ከተሞች በማዘመን የተጫወተውን ሚና ማድነቃቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት መረጃ ያመለክታል፡፡ ከቻይና ጭምር የሌላ ሀገራት ቱሪስቶችን በሰፊው የመሳብ ትልም እውን ለማድረግ ሆቴሎችን፣ አውሮፕላን ማረፊያዎችን እና ተያያዥ አገልግሎቶችን መገንባት ቁልፍ እንደሆነም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አውስተዋል።
EBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች