ኢትዮጵያ ፈተናዎችን ተቋቁማ ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበች መሆኗን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ረገድ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚዋ ሀገር መሆኗንም አንስተዋል፡፡ ሀገሪቱ ያላት የካፒታል ገበያ፣ የተወሰዱ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች እና ሌሎች ሁኔታዎች፤ ለኢንቨስትመንት ተመራጭ እንደሚያደርጓትም ጠቁመዋል፡፡ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በበኩላቸው ሀገሪቱ የዲጂታል ኢኮኖሚን በመገንባት ሂደት ላይ መሆኗን መናገራቸውን ፋና ዘግቧል፡፡ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፤ በጤናው ዘርፍ ለመሰማራት የሚያስችሉ መሰረተ-ልማቶች የተሟሉ መሆናቸውን አመላክተዋል፡፡የኢትዮ-ቻይና ከፍተኛ የቢዝነስ ፎረም በቻይና ቤጂንግ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡
EBC
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።