የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በግብርናው ዘርፍ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተፕራይዞችን ለማደራጀት እና ወደ ስራ ለማስገባት ተስማምተዋል፡፡ ስምምነቱን የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል እና የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ዮሃንስ አያሌው (ዶ/ር) ተፈራርመውታል፡፡ ሚኒስቴሩ ሥራ ፈጣሪዎችን በማበረታታት ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ ከባንኩ ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ተናግረዋል፡፡ “በግብርናው ዘርፍ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በበቂ መጠን የሉም” ያሉት ሚኒትሯ፤ ስምምነቱ በመስኩ የበለጠ የሥራ ዕድል እንዲፈጠር እንደሚያስችል ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ዮሃንስ አያሌው (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ባንኩ ከሚኒስቴሩ ጋር በመሆን በተያዘው በጀት ዓመት ወጣቶችን ወደ ስራ ለማስገባት አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረጉን አስታውቀዋል፡፡ ለመርሐ-ግብሩ በአጠቃላይ 43 ሚሊዮን ዶላር ሥራ ላይ እንደሚውል የገለጹት ዮሃንስ አያሌው (ዶ/ር)፤ ባንኩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት ፋይናንሱን ተደራሽ እንደሚያደርግ አብራርተዋል። የአፍሪካ ልማት ባንክ ለስራ ዕድል ፈጠራ ፋይናንስ የሚያቀርብ ሲሆን በኢትዮጵያ ልማት ባንክ በኩል ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ተደራሽ እንደሚሆን መገለጹን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
EBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች