የኢትዮጵያ የምግብ ዋስትና ሥራዎች ሀገሪቱ ራሷን ችላ ለምትቆምበት መፃዒ ተስፋ በር የሚከፍት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ የትስስር ገጻቸው ላይ “የኢትዮጵያ የምግብ ዋስትና ሥራዎች እና የምግብ ሉዓላዊነት መንገድ በጠንካራ ትብብሮች ተሻግሮ ሀገራችን በአየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮቶች ሳትበገር ራሷን ችላ ለምትቆምበት መፃዒ ተስፋ በር የሚከፍት ነው” ብለዋል፡፡ በዘላቂ የግብርና ሥራ፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እና የአቅም ግንባታ ሥራ፤ ኢትዮጵያ ምርታማነትን ማላቅ፣ የአዝርዕት አይነትን ማብዛት ብሎም የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን ማሻሻል እንደምትችልም ገልጸዋል፡፡ እንደዚህ አይነቶቹ ትብብሮች የማኅበረሰብን አቅም ከፍ እንደሚያደርጉ፣ የኢኮኖሚ ዕድሎችን እንደሚፈጥሩ እና ፈጠራን እንደመያበረታቱም ጠቁመዋል፡፡ ይህም ኢትዮጵያን በዘላቂ የምግብ ሥርዓት መሪ እንደሚያደርጋት እና የበለፀገ የምግብ ዋስትና የተረጋገጠበት መፃዒ ጊዜን ለህዝቡ እንደሚያረጋግጥም አመላክተዋል፡፡
EBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች