ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር አሻራቸውን አኑረዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ለታሪካዊው የችግኝ ተከላ በዛሬዋ ታሪካዊት ቀን በተፈጥሮ ስጦታ፣ በማዕድን ሃብትና ለም ምድር በሚታወቀው የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል አሶሳ ከተማ ተገኝተናል ብለዋል።በዛሬው ሁነት መጨረሻ በመላው ሀገራችን ባለፉት አምስት ዓመታት የተተከልናቸው ችግኞች ወደ 40 ቢሊየን ይደርሳሉ ሲሉም ገልጸዋል፡፡ባለፈው ዓመት ከተተከሉት ችግኞች 50 ከመቶው በምግብ ዋስትና፣ አፈር ጥበቃ እና የመሬት መራቆት ላይ አስተዋፅዖ እንዲያደርጉ የተተከሉ እንደነበሩ አስታውሰዋል፡፡በቀጣይም እንደ አባይ ተፋሰስ ባሉ አካባቢዋች ችግኞችን በመትከል የውሃ ጥበቃ ሥራን ልንደግፍ ይገባል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፡፡
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።