ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር አሻራቸውን አኑረዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ለታሪካዊው የችግኝ ተከላ በዛሬዋ ታሪካዊት ቀን በተፈጥሮ ስጦታ፣ በማዕድን ሃብትና ለም ምድር በሚታወቀው የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል አሶሳ ከተማ ተገኝተናል ብለዋል።በዛሬው ሁነት መጨረሻ በመላው ሀገራችን ባለፉት አምስት ዓመታት የተተከልናቸው ችግኞች ወደ 40 ቢሊየን ይደርሳሉ ሲሉም ገልጸዋል፡፡ባለፈው ዓመት ከተተከሉት ችግኞች 50 ከመቶው በምግብ ዋስትና፣ አፈር ጥበቃ እና የመሬት መራቆት ላይ አስተዋፅዖ እንዲያደርጉ የተተከሉ እንደነበሩ አስታውሰዋል፡፡በቀጣይም እንደ አባይ ተፋሰስ ባሉ አካባቢዋች ችግኞችን በመትከል የውሃ ጥበቃ ሥራን ልንደግፍ ይገባል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፡፡
FBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች