በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተረክሂን የተመራ ልዑካን ቡድን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደርን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝቷል፡፡ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ ሀገራዊ የሳይበር ደህንነትን ለማረጋገጥ በተቋሙ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን አስመልክቶ ለቡድኑ ገለጻ አድርገዋል። በሳይበር ደህንነት ዘርፍ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተጀመረውን ሁሉን አቀፍ የትብብር ስራ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እንደሚሰራም ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተረክሂን የጉብኝቱ ዓላማ የኢትዮጵያን የሳይበር ደህንነት ልምድ መመልከትና ሁለቱ ሀገራት በዘርፉ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር መሆኑን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ በሳይበር ደህንነት ዘርፍ፤ በተለይም ደግሞ የቴክኖሎጂና የዕውቀት ባለቤትነትን በማረጋገጥ ረገድ ከፍተኛ ስራ መስራቷን ከጉብኝቱ መረዳታቸውን ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያ የሳይበር ደህንነቷን እና ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ በምታደርገው ጥረት ሩሲያ ያላትን ልምድ ከማካፈል ጀምሮ በጋራ ለመስራት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላት አምባሳደሩ መናገራቸውን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት
EBC
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።