በአቅርቦት እጥረት ምክንያት ለመጪው በዓል በሚውሉ ምርቶች ላይ የዋጋ መናር እንዳይፈጠር በቂ ዝግጅት መደረጉን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡ከ115 ሚሊዮን ሊትር በላይ የምግብ ዘይት ጅቡቲ መድረሱን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ በቀናት ውስጥ ወደ ምርት ማዕከል እንደሚገቡም ነው የጠቆሙት፡፡አክለውም ሌሎች መሰረታዊ የፍጆታ ምርቶች ወደ ምርት ማዕከል እንደሚገቡም ጠቅሰዋል፡፡ዝቅተኛው የማህበረሰብ ክፍል እንዳይጎዳ መንግስት በጥንቃቄ እየሰራ መሆኑን ያነሱት ሚኒስትሩ፤ ስራው ውጤታማነት እያሳየ መሆኑን ገልጸው፣በምርት በእጥረት ምክንያት የሚፈጠር የዋጋ ንረት እንደማይኖር ነው የተናገሩት፡፡
EBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።