የጋምቤላ ህዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባዔ ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አድርጎ ሾሟል። የክልሉ ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 6ኛ ዙር 3ኛ የስራ ዘመን 2ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ነው ለርዕሰ መስተዳድሯ ሹመቱን የሰጠው፡፡ አዲስ ሹመት የተከናወነው ወቅቱ የሚጠይቀውን አሻጋሪ የለውጥ አመራር በማምጣት የህዝቡ የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ፍላጎቶች በተገቢው መንገድ ምላሽ እንዲያገኙ ለማስቻል እንዲሁም የቀድሞው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ በገዥው ፓርቲ ለሌላ ተልዕኮ በመፈለጋቸው መሆኑም ተጠቅሷል። ወይዘሮ ዓለሚቱ አሞድ ቀደም ሲል የክልሉ ምክትል አፈ- ጉባኤ፣ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ በመሆንና በሌሎች የተለያዩ ከፍተኛ የስራ ኃላፊነቶች ሲያገለግሉ መቆየታቸው ተጠቁሟል፡፡ ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ በክልሉ ታሪክ የመጀመሪያዋ ሴት ርዕሰ መስተዳድር መሆናቸውም ተገልጿል። በሚፍታህ አብዱልቃድር
EBC
More Stories
ባለፉት ሦስት ዓመታት ለሰብዓዊ ድጋፍ በሚል የገባ ስንዴ የለም – አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር)
በገጠሩ የሀገሪቱ አካባቢዎች መንግስት የሚዘረጋቸውን የተለያዩ ኢንሸቲቦችን ቀድሞና ፈጥኖ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር የተሻሉ አፈጻጸሞች መታየታቸው ተገለፀ ።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ6 ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ