በአንካራ በተካሄደው ድርድር ኢትዮጵያ የባሕር በር እንደሚያስፈልጋት የአለም አቀፉ ማህበረሰብ የተረዳበት መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ መንግስት ሰላማዊ እና ህጋዊ በሆነ መንገድ የባሕር በር በጋራ የማልማት እና የመጠቀም እንቅስቃሴውን እንደሚገፋበት ተነግሯል፡፡ ይህ የተገለፀው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብዩ ተድላ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት ሳምንታዊ መግለጫ ነው፡፡ በሳምንታዊ መግለጫውም በቱርክ አንካራ በሶማሊያ እና ኢትዮጵያ የተደረገው ሁለተኛው ዙር የሁለትዮሽ ድርድር ተስፋ ሰጭ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
EBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች