በአንካራ በተካሄደው ድርድር ኢትዮጵያ የባሕር በር እንደሚያስፈልጋት የአለም አቀፉ ማህበረሰብ የተረዳበት መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ መንግስት ሰላማዊ እና ህጋዊ በሆነ መንገድ የባሕር በር በጋራ የማልማት እና የመጠቀም እንቅስቃሴውን እንደሚገፋበት ተነግሯል፡፡ ይህ የተገለፀው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብዩ ተድላ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት ሳምንታዊ መግለጫ ነው፡፡ በሳምንታዊ መግለጫውም በቱርክ አንካራ በሶማሊያ እና ኢትዮጵያ የተደረገው ሁለተኛው ዙር የሁለትዮሽ ድርድር ተስፋ ሰጭ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
EBC
More Stories
ሮቦቶችም ተማሪ ሆኑ! በቻይና የተከፈተው የዓለማችን መጀመሪያው የሮቦቶች ትምህርት ቤት አስገራሚ እውነታ
የግል ጄታቸውን ለሕዝብ አምቡላንስ አገልግሎት የለገሱት ጋናዊው ቱጃር
ፌራሪ የመጀመሪያውን ባለ 5 መቀመጫ የኤሌክትሪክ መኪና አስተዋወቀ