ኢትዮጵያና ሶማሊያ ሁለተኛውን ዙር ውይይት ማድረጋቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አስታውቀዋል፡፡የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት÷በቱርክ አመቻችነት በኢትዮጵያና በሶማሊያ መካከል 2ኛ ዙር ዉይይት በአንካራ መካሄዱን ገልጸዋል።አምባሳደር ታዬ የቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሃከን ፊዳን ከውይይቱ በፊት ኢትዮጵያን በመጎብኘታቸው ምስጋና አቅርበዋል።“የኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ያላት ህጋዊ ፍላጎትም በሰላማዊ መንገድ ከጎረቤቶቻችን ጋር በመተባበር እንደሚፈፀም እርግጠኛ ነኝ” ሲሉም ገልጸዋል።
FBC
More Stories
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአረፋ(ዒድ አል አድሃ) በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት
መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም የተገቡ ቃሎች አንድ በአንድ እየተተገበሩ ናቸው – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን ታላቁን የክብር ኒሻን ለቢል ጌትስ ሸለሙ