ኢትዮጵያና ሶማሊያ ሁለተኛውን ዙር ውይይት ማድረጋቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አስታውቀዋል፡፡የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት÷በቱርክ አመቻችነት በኢትዮጵያና በሶማሊያ መካከል 2ኛ ዙር ዉይይት በአንካራ መካሄዱን ገልጸዋል።አምባሳደር ታዬ የቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሃከን ፊዳን ከውይይቱ በፊት ኢትዮጵያን በመጎብኘታቸው ምስጋና አቅርበዋል።“የኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ያላት ህጋዊ ፍላጎትም በሰላማዊ መንገድ ከጎረቤቶቻችን ጋር በመተባበር እንደሚፈፀም እርግጠኛ ነኝ” ሲሉም ገልጸዋል።
FBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች